የሳይበር ጥቃት መከላከል ወትሮ ዝግጁነት በማረጋገጥ ረገድ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ

Sisälletyt portletit

Sisältöjulkaisija

ኢመደአ ለሜቄዶንያ የአረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የ2018 አዲስ ዓመትን በማስመልከት ድጋፍ አደረገ።

ኢመደአ ለሜቄዶንያ የአረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የ2018 አዲስ ዓመትን በማስመልከት ድጋፍ አደረገ። pe, 5 syyskuuta 2025

ድሮን አምርቶ እስከ መታጠቅ

ድሮን አምርቶ እስከ መታጠቅ pe, 5 syyskuuta 2025

እንኳን ለ1 ሺህ 500ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

እንኳን ለ1 ሺህ 500ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! pe, 5 syyskuuta 2025

ኢትዮጵያ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ የገነባችው አቅም በተሞክሮነት ሊወሰድ የሚችል እንደሆነ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ የገነባችው አቅም በተሞክሮነት ሊወሰድ የሚችል እንደሆነ ተገለጸ pe, 29 elokuuta 2025

Sisältöjulkaisija

null የሳይበር ጥቃት መከላከል ወትሮ ዝግጁነት በማረጋገጥ ረገድ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ

ስኬታማ እና ዘላቂ የሳይበር መከላከል ወትሮ ዝግጁነት በማረጋገጥ ረገድ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ሀገራዊ የሳይበር ጥቃት መከላከል ወትሮ ዝግጁነት ላይ ያተኮረ ውይይት ከተለያዩ ባለድሻ አካላት ጋር (የጸጥታና ደህንነት ተቋማት፣ ቁልፍ መሰረተ ልማት የሚያስተዳድሩ ተቋማት፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ ሚዲያ ወ.ዘ.ተ) አካሂዷል፡፡

የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኢመደአ ም/ዋና ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ሃኒባል ለማ እንዳሉት ሀገራችን አሁን ካለችበት ወቅታዊ የጂኦ-ፖለቲካል ሁኔታ አኳያ፤ በተለይም ከታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ጋር ተያይዞ የውስጥና የውጭ ስጋቶች መበራከትን ተከትሎ ተቋማት የሳይበር ደህንነታቸውን ከመጠበቅ አኳያ አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባቸው ገልጸዋል፡፡

ሀገራዊ የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የሚቻለው ተቋማት የራሳቸውን የሳይበር ደህንነት ማረጋገጥ ሲችሉ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ሃኒባል፤ ከዚህ አኳያ ተቋማት ያላቸውን የዲጂታል ሃብት እና መሰረተ ልማት በአግባቡ መለየትና የአደጋ ግምገማ (Risk Assessment) ማካሄድ፤ የ24/7 የክትትልና ምላሽ አቅምን ማሳደግ፣ የሰራተኞችን ግንዛቤ በተከታታይ ስልጠና ማሳደግ፣ እንዲሁም ማንኛውንም የጥቃት ሙከራ ለብሔራዊ የሳይበር ደህንነት ማስተባበሪያ ማዕከል ሪፖርት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየትና ጥያቄዎች ሰፊ ማብራሪያና ምላሻ ከመድረኩ የተሰጠ ሲሆን፤ ወጥነት ባለው መልኩ እንዲህ ዓይነት መድረኮች እንደሚካሄዱና በቀጣይ ሁሉም ተቋማት እንደሚሰጡት የአገልግሎት ዓይነትና ስፋት በሚቀመጠው መስፈርት ልክ የሳይበር መከላከል ከፍል ሊኖራቸው እንደሚገባ ተመላክቷል፡፡