ኤጀንሲዉ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና በመረጃ ደህንነት ዙሪያ በጋራ ለመስራት ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

 

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢመደኤ) ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ጋር ዘመናዊ ግብይት ስርአትን ለማሳለጥ በሚያግዙ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና በመረጃ ደህንነት ዘርፍ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ፈራረሙ።

በመግባቢያ ስምምነቱ ላይ የተገኙት የኢመደኤ ዋና ዳይሬክተር / ሹመቴ ግዛዉ ኢመደኤ በአዋጅ ከተሰጡት ሃላፊነቶች ዋናዉ የሃገሪቱን የኢንፎርሜሽን እና የኢንፎርሜሽን መሰረተ ልማት ደህንነት ማስጠበቅ መሆኑን አዉስተዉ እንደ ኢትዮጵያ ምርት ገበያ አይነት ወሳኝ ሃገራዊ ተቋምን ደህንነት ማርጋገጥ ተቀዳሚ ተግባሩ ነዉ ብለዋል።  

ኢመደኤ ኢትዮጵያ ምርት ገበያ የመረጃ ፍስት እንዳይስተጓጎል ከመነሻዉ ጀምሮ እስከ መዳረሻዉ ሚስጥራዊንቱን እና ደህንነቱን ጠብቆ እንዲዘዋወር ማድርግ ይገባል ያሉት ዶ/ር ሹመቴ ኢመደኤም የመረጃን ወሳኝ ሃብትነት በመረዳት የኢትዮጵያ ምርት ገበያን በሚያስፈልገዉ ሁሉ ከጎናቸዉ እንደሚሆን ጠቁመዋል።  

 

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ነገራ በበኩላቸዉ ከኢመደኤ ጋር ዛሬ የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት ተቋማቸዉ ለያዘዉ የአፍሪካ የልህቀት ማእከልነት ግስጋሴ እንደሚያቀላጥፍ እና ምርት ገበያዉ ወደፊት ለሚጀምራቸዉ ወሳኝ ስራዎች የቴክኖሎጂ አቅምን እና ብቃትን ለማጎልበት የላቀ መሆኑን ተናግረዋል።

አሁን ላይ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ 25 ሚሊዮን ህዝብ በላይ በቀጠታም ሆነ በተዘዋዋሪ በሚደረጉ የግብይት ስርአት ተጠቃሚ መሆናቸዉን የገለጹት የምርት ገበያዉ ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ወንድማገኝ በየአመቱ 40 ቢሊዮን ዋጋ ያላቸዉን መረቶች ተቋማቸዉ እንደሚያገበያይ ገልጸዋል። ኢመደኤ ከዚህ ቀደም ከተቋማቸዉ ጋር በጋራ እየሰራ መቆየቱን ያወሱት አቶ ወንድማገኝ በቀርቡ በክልሎች ወደስራ ከገቡ ሰባት ግብይት ማእከላትን ኢመደኤ የደህንነት ፍተሻ ካደረገ በኋላ ወደስራ መገባቱን በማሳያነት አንስተዋል።

በዚህ የመግባቢያ ስምምነት መሰረት ኢመደኤ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የስራ ክፍሎችን አግልግሎት አዉቶሜትድ የማድረግ፣ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፖሊሲ ማዘጋጀት፣ የሳይበር ኢዲት እና ምዘና ማከናወንን ጭምሮ የሰዉ ሃይል አቅም ግንባታ ድጋፍ ያደርጋል። 

 

Asset Publisher


የቅርብ ዜናዎች