የዲያስፖራው ተሳትፎ፣ ለሀገራችን የሳይበር ደህንነት!!

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

 

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ /ኢመደኤ/ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ ከዲያስፖራው ማህበረሰብ ጋር ሰኞ ጥር 9 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በኤጀንሲው ዋና መ/ቤት የምክክር መድረክ ያካሂዳል፡፡

በዕለቱ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ የእውቀትና ቴክኖሎጂ ባለቤትነት በማረጋገጥ፣ ሥልጠናዎችን በመስጠት፣ በሳይበር ደህንነት ኢንቨስት በማድረግ እና በሌሎች የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፎች የዲያስፖራው ማህበረሰብ ሊኖረው በሚችለው አስተዋጽኦ ዙሪያ ገለጻ፣ ምክክር እንዲሁም የዲጂታል ኤግዚቢሽን እና የታለንት ማዕከል ጉብኝት ይደረጋል፡፡

ከኤጀንሲው ጋር ከዚህ ቀደም በተለያዩ አግባቦች ግንኙነት የፈጠራችሁም ይሁን ሌሎች ከኤጀንሲው ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎቱ ያላችሁ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አካላት በኤጀንሲው ዋና መ/ቤት /ቦሌ ወሎ ሰፈር ከቴሌ ማሰልጠኛ አጠገብ/ በሚካሄደው የውይይት መድረክ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃል ።

ለውይይቱ ወደ ተቋሙ ከመምጣታችሁ አስቀድማችሁ በስልክ ቁጥር /+251944762100፣ +251910012912 ወይም +251904049633/ በመደወል እንድትመዘገቡ ስንል በአክብሮት እንጠይቃለን።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ!