በሳይበር ምህዳሩ ላይ ራስን ከማንነት ስርቆት የምንከላከልባቸው መንገዶች የትኞች ናቸው?

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]



በሳይበር አለም ከሚፈፀሙ የሳይበር ጥቃቶች መካከል አንዱ የሆነው የማንነት ስርቆት (identity theft) ነው፡፡ይህ የጥቃት አይነት የሳይበር ጥቃት በማሀበረሰቡ ላይ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነ-ልቦናዊ ችግሮችንና ጫናዎችን ያስከትላሉ፡፡

ማንነትን ተገን ተደርገዉ ከሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ራስን ለመከላከል ሊወሰዱ ከሚገቡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መተግበር ወሳኝ ነዉ።

 የምንጠቀመውን የበይነ-መረብ ፕሮቶኮል (IP address) ደህንነት ማረጋገጥ፤

 በምንጠቀማቸው የማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎቶች ላይ የሁለት ወገን
ማረገጋጫን (two factor authentication ) ተግባራዊ ማድረግ ፤

 የፋይናንስ ክሬዲት ሪፖርቲንግ አገልግሎት መመዝገብና መጠቀም፤

 የህዝብ ዋይ ፋይና ሌሎች ነፃ በይነመረብ (internet) አገልግሎት መስጫ አለመጠቀም፤

 ጠንካራና በቀላሉ የማይገመት የይለፍ-ቃል መጠቀም (password) መጠቀም፤

 የምንጠቀመውን ድረ-ገጽ(website) አድራሻ ትክክለኛነት ማረጋገጥ ወይም Uniform resource locater (URL) ደህንነትና ትክክለኛ የድረገጽ ፕሮቶኮል እየተጠቀምን መሆኑን ማረጋገጥ ፤

 የምንጠቀማቸውን የማህበራዊ ሚዲያዎች ግላዊነት( privacy) ወይም ደህንነት ማረጋገጥ፤

 የባንክ አካውንት ዶክመንቶችና ሌሎች ጠቃሚ የግል መረጃዎችን መጠበቅ፤

 በተለያዩ አዳዲስ ድረ-ገጾች ላይ መረጃዎችንና ሊንኮችን ለመክፈት የግል መረጃዎችን ሲጠየቁ መረጃዎችን ከመስጠት መቆጠብ፤
 ሌሎች ማንዋል መረጃዎቻችንን ለምሳሌ፡-የትምህርት ማስረጃዎች፣ የነዋሪነት መታዎቂያና የተለያዩ የግል መረጃዎችን መጠበቅ ከጠፉ ደግሞ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት በማደረግ በቶሎ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል።