ኢመደአ፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት እና የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት በጋራ በመሆን የኢፍጣር መርሐ- ግብር አካሄዱ፡፡

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) የሰላም ሚኒስቴር፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት እና የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት በጋራ በመሆን የኢፍጣር መርሐ- ግብር አካሄዱ፡፡

በመርሐ-ግብሩ ላይ የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ፣ የሰላም ሚኒስትር አቶ መሃመድ ኢድሪስ፣ የአርተፍሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ወርቁ ጋቸና፣ እንዲሁም ሚንስትር ዴታዎች፣ የተቋማቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች፣ መካከለኛ አመራሮችና ሰራተኞች ተገኝተዋል።

በተጨማሪም በመርሃ ግብሩ የሀይማኖት ተቋማት ጉባዬ ጠቅላይ ጸሃፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ዋና ጸሃፊ ሼህ ሃሚድ ሙሳ፣ ኡስታዝ በድሩ ሁሴንን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተሳትፈዋል።

ከኢፍጣር መርሃ ግብሩ ጎን ለጎን ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም አከናዉኗል።

Publicador de Conteúdos e Mídias


የቅርብ ዜናዎች