ኢመደአ በቀጨኔ ሴት ሕጻናት ጊዜያዊ ማቆያና ማቋቋሚያ ማዕከል ለሚገኙ ታዳጊና ወጣት ሴቶች የማዕድ ማጋራት እና የትምህርት ቁሳቁስ መግዣ ድጋፍ አደረገ

Nested Applications

Asset Publisher

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) “አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቪ"ን አስጀመሩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) “አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቪ"ን አስጀመሩ Tue, 23 Jul 2024

የከተማ አስተዳደሩ የዲጂታል ካዳስተር ሥርዓት ከመሬት ጋር ተያይዘው የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ለመፍታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገለጸ

የከተማ አስተዳደሩ የዲጂታል ካዳስተር ሥርዓት ከመሬት ጋር ተያይዘው የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ለመፍታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገለጸ Fri, 19 Jul 2024

ዲጂታል ዲፕሎማሲ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለዲፕሎማሲ ባለው አበርክቶ ዙሪያ ለአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ሥልጠና ተሰጠ

ዲጂታል ዲፕሎማሲ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለዲፕሎማሲ ባለው አበርክቶ ዙሪያ ለአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ሥልጠና ተሰጠ Tue, 16 Jul 2024

ኢመደአ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

ኢመደአ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ Tue, 16 Jul 2024

Asset Publisher

null ኢመደአ በቀጨኔ ሴት ሕጻናት ጊዜያዊ ማቆያና ማቋቋሚያ ማዕከል ለሚገኙ ታዳጊና ወጣት ሴቶች የማዕድ ማጋራት እና የትምህርት ቁሳቁስ መግዣ ድጋፍ አደረገ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) የ2016 አዲስ አመት መቀበያን እና የትውልድ ቀንን ምክንያት በማድረግ በቀጨኔ የሴት ሕጻናት ጊዜያዊ ማቆያና ማቋቋሚያ ማዕከል ውስጥ ለሚገኙ 104 (አንድ መቶ አራት) ለሚሆኑ ታዳጊና ወጣት ሴቶች የምሳ ግብዣ፣ የትምህርት ቁሳቁስ መግዣ፣ እና ለማዕከሉ የሚያስፈልጉ የተለያዩ የቢሮና የጽዳት ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ፡፡

በአስተዳደሩ ዋና መ/ቤት በተደረገው የምሳ ግብዣ እና የትምህርት ቁሳቁስ መግዣ ድጋፍ ላይ የተገኙት የኢመደአ ም/ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ አስቴር ዳዊት ባስተላለፉት መልዕከት በቀጨኔ የሴት ሕጻናት ጊዜያዊ ማቆያና ማቋቋሚያ ማዕከል ውስጥ የሚገኙ ታዳጊና ወጣት ሴቶች መጪውን 2016 አዲስ አመት በብሩህ ተስፋና በደስታ እንዲቀበሉት በማሰብ የምሳ ግብዣ እና የትምህርት ቁሳቁስ መግዣ ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል፡፡ የተደረገው ድጋፍ በዋናነት ኢመደአ በማዕከሉ ውስጥ ለሚገኙ ታዳጊና ወጣት ሴቶች ያለውን አጋርነት ለማሳየት መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ አስቴር ሌሎች ተቋማትና ግለሰቦችም ይህንን በጎ ተግባር ሊቀጥሉበት ይገባል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሕጻናት ማቆያ ማዕከሉ የሚገኙ ታዳጊ ወጣት ሴቶች የነገ ሃገር ተረካቢ ዜጎች እንዲሆኑ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸውም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የቀጨኔ የሴት ሕጻናት ጊዜያዊ ማቆያና ማቋቋሚያ ማዕከል ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ደበበ ባስተላለፉት መልዕክት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ላደረገላቸው ድጋፍ አምስግነው፤ ኢመደአ የአገሪቱን የሳይበር ደህንነት ከማስጠበቅ ባሻገር ማህበራዊ ሃላፊነቱ በትክክል የሚወጣ ሕዝባዊ ተቋም እንደሆነ የሚያረጋግጥ በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የሕይወት ልምዳቸውን ያካፈሉት ዶ/ር ደረጄ ባስተላለፉት መልዕክት “ከወላጅ አልባ ሕጻናት ማሳደጊያ ማዕከል በመነሳት ትልቅ ደረጃ መድረስ እንደሚቻል የእኔ ሕይወት ሕያው ምስክር ነው” ብለዋል፡፡ በመሆኑም ታዳጊ ወጣት ሴቶች አሁን ያሉበትን ደረጃና ሕይወት ሳይሆን የነገ ሕልማቸውን ታሳቢ በማድረግ ጠንክረው እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡

በሌላም በኩል “የሸጋ ትውልድ ማሕበር” ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳሙኤል ገረመው በማዕድ ማጋራትና የድጋፍ መርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት በማዕከሉ ውስጥ የሚገኙ ታዳጊና ወጣት ሴቶች ያላቸውን እምቅ አቅምና ልዩ ተሰጥኦ እንዲያወጡና ለትውልድ የሚተርፍ ሥራ እንዲሰሩ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍና ስልጠና እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ በኢመደአ የኢትዮ ሳይበር ታለንት ልማት ማዕከል የሚገኙ ባለ ልዩ ተሰጥኦ ታዳጊ ወጣቶች በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ለታዳጊና ወጣት ሴቶቹ ልምዳቸውንና ተሞክሯቸውን አካፍለዋል፡