አስተዳደሩ ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ የስራ አመራር አባላት በሳይበር ደህንነት ዙሪያ ስልጠና ሰጠ

Nested Applications

Asset Publisher

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) “አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቪ"ን አስጀመሩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) “አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቪ"ን አስጀመሩ Tue, 23 Jul 2024

የከተማ አስተዳደሩ የዲጂታል ካዳስተር ሥርዓት ከመሬት ጋር ተያይዘው የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ለመፍታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገለጸ

የከተማ አስተዳደሩ የዲጂታል ካዳስተር ሥርዓት ከመሬት ጋር ተያይዘው የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ለመፍታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገለጸ Fri, 19 Jul 2024

ዲጂታል ዲፕሎማሲ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለዲፕሎማሲ ባለው አበርክቶ ዙሪያ ለአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ሥልጠና ተሰጠ

ዲጂታል ዲፕሎማሲ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለዲፕሎማሲ ባለው አበርክቶ ዙሪያ ለአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ሥልጠና ተሰጠ Tue, 16 Jul 2024

ኢመደአ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

ኢመደአ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ Tue, 16 Jul 2024

Asset Publisher

null አስተዳደሩ ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ የስራ አመራር አባላት በሳይበር ደህንነት ዙሪያ ስልጠና ሰጠ

 

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 16 ፣ 2014 የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ የስራ አመራር አባላት በሳይበር ደህንነት ዙሪያ የግማሽ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡

በስልጠናው መርሀ ግበር ላይ የተገኙት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሳይበር ደህንነት ጉዳይ ትኩረት ባለመሰጠቱ በርካታ ጉዳቶች እየደረሱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ ሶስት መሰረታዊ ነገሮችን ማሟላት ይጠይቃል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፤እነዚህም እውቀትና ክህሎት ያለው የሰው ሃይል፣የዘመኑ ቴክኖሎጂዎችና ትክክለኛ የአሰራር ስርዓት መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ይህ ሲሟላም የሳይበር ደህንነት አስተማማኝ ደረጃ ደርሷል ማለት እንደሚቻል ዶ/ር ሹመቴ ገልፀዋል፡፡

በቀጣይም አስተዳደሩ ተመሳሳይ ስልጠና ለባንኩ አመራሮችና ሰራተኞች ለመስጠት ፈቃደኛ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚደንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው በበኩላቸው የኢንፎርሜሽን ዲጂታል ስርዓት የሀገራት መወዳደሪያ ጡንቻ በሆነበት በዚህ ወሳኝ ወቅት የተቋማት መረጃን ከማንኛውም አይነት የሳይበር ጥቃት መጠበቅ ትኩረት የሚሻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ሀገራት ሉአላዊነታቸውንና አጠቃላይ ህልውናቸውን አረጋግጠው ለመኖር የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅምን መገንባት አማራጭ ሳይሆን ግዴታ የሆነበት ዘመን ላይ እንገኛለን ያሉት የባንኩ ፕሬዝደንት፤ከዚህ አንጻር የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ስልጠናውን ለመስጠት ላሳየው ተነሳሽነት ምስጋናቸውንም አቅርበዋል፡፡