የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ኤምባሲ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና የሚዲያ ጉዳዮች ሃላፊ ታላል አል አዘሪ ጋር ተወያዩ

Nested Applications

Asset Publisher

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ አመራሮች የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን ጎበኙ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ አመራሮች የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን ጎበኙ Fri, 24 Nov 2023

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የሸገር ከተማ አስተዳደር የሥራ ውል ስምምነት ተፈራረሙ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የሸገር ከተማ አስተዳደር የሥራ ውል ስምምነት ተፈራረሙ Mon, 27 Nov 2023

ኢትዮጵያ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ ከሀገራት ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኗ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ ከሀገራት ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኗ ተገለጸ Fri, 17 Nov 2023

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በኢትዮጵያ የማልታ ኤምባሲ ጋር በመተባበር በሳይበር ዲፕሎማሲ ዙሪያ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በኢትዮጵያ የማልታ ኤምባሲ ጋር በመተባበር በሳይበር ዲፕሎማሲ ዙሪያ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ Mon, 27 Nov 2023

Asset Publisher

null የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ኤምባሲ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና የሚዲያ ጉዳዮች ሃላፊ ታላል አል አዘሪ ጋር ተወያዩ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ኤምባሲ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና የሚዲያ ጉዳዮች ሃላፊ ከሆኑት ታላል አል አዘሪ ጋር በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡

በዉይይቱም የሳይበር ቴክኖሎጂ ባለቤትነትን በማረጋገጥና በዘርፉ ያለዉን የሰዉ ሃይል እጥረት በመቅረፍ ረገድ በጋራና በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡

ኢመደአ የኢትዮጵያን የሳይበር የቴክኖሎጂ ባለቤትነትን ለማረጋገጥ እየሰራ ያለዉ ስራ ለሌሎች አፍሪካ አገራት ምሳሌ ሊሆን የሚችል መሆናቸዉን የጠቀሱት ታላል አል አዘሪ ይህ መልካም ተሞክሮ ወደ ሌሎች አፍሪካ አገራት መስፋት የሚገባዉ መሆኑን ገልጸዋል። አያይዘውም በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ኤምባሲ ከኢመደአ ጋር በሳይበር ደህንነት ዘርፍ በይበልጥ በታዳጊዎች የሳይበር ታለንት ልማት ላይ በትብብር መስራት ፍላጎት እንዳለዉ ሚስተር ታላል ገልጸዋል።

የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በበኩላቸው ኢመደአ በሳይበር ቴክኖሎጂ ባለቤትነት እንዲሁም በሳይበር ታለንት ልማት ያካበተውን ተሞክሮ ለሌሎች የአፍሪካ ሐገራት ለማካፈል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ሰለሞን ሶካ ከታላል አል አዘሪ ጋር ካደረጉት ውውይት ባሻገር ኢመደአ ሐገራዊ የቴክኖሎጂ እና የእውቀት ባለቤትነትን በማረጋገጥ ረገድ እየሰራቸው የሚገኙ ሥራዎችን፤ የኢትዮ ሳይበር ታለንት ልማት ማዕከልን፤ እና ሌሎች ተቋማዊ ምርትና አገልግሎቶችን አስጎብኝተዋቸዋል፡፡