የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ኤምባሲ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና የሚዲያ ጉዳዮች ሃላፊ ታላል አል አዘሪ ጋር ተወያዩ

Nested Applications

Asset Publisher

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) “አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቪ"ን አስጀመሩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) “አምስት ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቪ"ን አስጀመሩ Tue, 23 Jul 2024

የከተማ አስተዳደሩ የዲጂታል ካዳስተር ሥርዓት ከመሬት ጋር ተያይዘው የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ለመፍታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገለጸ

የከተማ አስተዳደሩ የዲጂታል ካዳስተር ሥርዓት ከመሬት ጋር ተያይዘው የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን ለመፍታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገለጸ Fri, 19 Jul 2024

ዲጂታል ዲፕሎማሲ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለዲፕሎማሲ ባለው አበርክቶ ዙሪያ ለአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ሥልጠና ተሰጠ

ዲጂታል ዲፕሎማሲ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለዲፕሎማሲ ባለው አበርክቶ ዙሪያ ለአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ሥልጠና ተሰጠ Tue, 16 Jul 2024

ኢመደአ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

ኢመደአ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ Tue, 16 Jul 2024

Asset Publisher

null የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ኤምባሲ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና የሚዲያ ጉዳዮች ሃላፊ ታላል አል አዘሪ ጋር ተወያዩ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ኤምባሲ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና የሚዲያ ጉዳዮች ሃላፊ ከሆኑት ታላል አል አዘሪ ጋር በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡

በዉይይቱም የሳይበር ቴክኖሎጂ ባለቤትነትን በማረጋገጥና በዘርፉ ያለዉን የሰዉ ሃይል እጥረት በመቅረፍ ረገድ በጋራና በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡

ኢመደአ የኢትዮጵያን የሳይበር የቴክኖሎጂ ባለቤትነትን ለማረጋገጥ እየሰራ ያለዉ ስራ ለሌሎች አፍሪካ አገራት ምሳሌ ሊሆን የሚችል መሆናቸዉን የጠቀሱት ታላል አል አዘሪ ይህ መልካም ተሞክሮ ወደ ሌሎች አፍሪካ አገራት መስፋት የሚገባዉ መሆኑን ገልጸዋል። አያይዘውም በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ኤምባሲ ከኢመደአ ጋር በሳይበር ደህንነት ዘርፍ በይበልጥ በታዳጊዎች የሳይበር ታለንት ልማት ላይ በትብብር መስራት ፍላጎት እንዳለዉ ሚስተር ታላል ገልጸዋል።

የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በበኩላቸው ኢመደአ በሳይበር ቴክኖሎጂ ባለቤትነት እንዲሁም በሳይበር ታለንት ልማት ያካበተውን ተሞክሮ ለሌሎች የአፍሪካ ሐገራት ለማካፈል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ሰለሞን ሶካ ከታላል አል አዘሪ ጋር ካደረጉት ውውይት ባሻገር ኢመደአ ሐገራዊ የቴክኖሎጂ እና የእውቀት ባለቤትነትን በማረጋገጥ ረገድ እየሰራቸው የሚገኙ ሥራዎችን፤ የኢትዮ ሳይበር ታለንት ልማት ማዕከልን፤ እና ሌሎች ተቋማዊ ምርትና አገልግሎቶችን አስጎብኝተዋቸዋል፡፡