የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ከኢ.ፌዲ.ሪ. የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ጋር የተቋሙን ድረ-ገጽ ፖርታል አበልጽጎ ለማስረከብ የሚያስችል የሥራ ውል ስምምነት (Web Portal Development Service Agreement) ተፈራረመ፡፡

በስምምነቱ ላይ የኢመደአ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ባስተላለፉት መልዕክት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የድረ-ገጽ ፖርታሉን ደህንነቱን በጠበቀ መልኩ አበልጽጎ የሚያስረክብ ሲሆን በቀጣይ ሊጨመሩ ወይም ሊስተካከሉ የሚገቡ ነገሮች ካሉ በሁለቱ ተቋማት ተወካዮች አማከኝነት የሚከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢ.ፌዲ.ሪ. የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ድኤታ ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ በበኩላቸው ባስተላለፉት መልዕክት የቀረበውን የመጀመሪያ ዙር ጅምር ድረ-ገጽ ፖርታል ስራ አድንቀው ከፖርታል ልማቱ በተጨማሪ የአገልግሎቱን ሠራተኞች ይሳይበር ደህንነት ንቃተ ሕሊና ለማሳደግ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እንደሚሰጥም ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮ ሰላማዊት አክለው እንደተናገሩት የሁለቱ ተቋማት ትብብር ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነታቸው እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

Asset Publisher


የቅርብ ዜናዎች