የትምህርት ሚንስቴር ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢመደኤን ዋና መ/ቤት ጎበኙ

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

 

አዲስ አበባ ፤ የካቲት 8/2014: የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲን (ኢመደኤ) ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸው ወቅት የኤጀንሲውን የሳይበር ተሰጥዎ ልማት ማዕከልን፣ በኤጀንሲዉ ለምተዉ በዲጂታል ኤግዚብሽን ማዕከል የቀረቡ ምርት እና አገልግሎትን እንዲሁም የኢመደኤ ሠራተኞችና የኃላፊዎች ቢሮዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ሚኒስትሩ ከኢመደኤ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል። በዉይይታቸዉም የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ በሚያስችሉ የምርምር ፣ ልማት እና ስልጠናዎች ላይ በጋራ መስራት በሚያስችላቸዉ ጉዳይ መክረዋል።